የቪክቶሪያ ኦርቶዶክስ ምዕመናን የምናመልክበት ህንጻ፣ የሚቀድልን ካህን፣ የምናነግሰው ታቦት አልነበረንም። ከቫንኮቨር ኆኅተ ሰማይ ቅድስት ማርያም ወንድሞች እየመጡ በጸሎት ይራዱን ነበር እንጂ። ለዚህም የምዕመናንን ቤት ጭምር እንጠቀም ነበር። ጊዜው 2008 (እ.ኤ.አ) ለጸሎት ስንጠቀምበት በነበረው 1100 ኮልቪሌ መንገድ ላይ የሚገኘውን የዩክሬናውያን ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያንን መናገሻ አድርገን በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ የወንድሞችና የእህቶች ጸሎት ሲሰማ በብጹእ አባታችን አቡነ ማቲያስ መልካም ፈቃድና ቡራኩ የታላቁና ገናናው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ታቦት ገባልን። የደብራችንንም ስም ወደፊት ሊመጣ ስላለው ተገብተው ብጹእ አባታችን ዳግማዊ ቁልቢ መንበረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ብለው ሰየሙት።
current status and details
ቤተ ክርስቲያኗ ስለሚከተሉት ዓላማዎች ስትል ተቋቁማለች